ከተሜነት
1.መግቢያ
አዲስ አበባ ከተማ ምንም እንኳን ከሌሎች የአሪካ ከተሞች ጋር ስትነጻጸር ዕድሜዋ አጭር ቢሆንም የአፈሪካ መዲና ብቻ ሳትሆን ዓለም አቀፍ የዲፕሎማቲክ መሆን ችላለች፡፡ የከተማቱ ዋና ከተመ መሆን ያልተዋተላቸው አንዳንድ ሀገራት በየጊዜው ያልተሟላውን መሰረተ ልማት፣የተንቀራፈፈውን የአገልግሎት ዘርፍ እነቀሱ በማውጣት በየጊዜው ተቀናቃኝነታቸውን ማሳየታቸው አልቀረም፡፡ ክርክሩን መሪዎቻችን ማሸነፍ የቻሉት የሚነሳው የመከራከሪያ ነትብ ስህተት በመሆኑ አልም ከሌሎች የተሻለች መሆን ስለቻለች አይደለም፡፡ ይልቁኑ አፍሪካውያን ለነጻነታቸው ያደርጉት የነበረውን ትግል ማገዝ በመቻልዋና ለአፍሪካ አንድነት መቋቋም በሰጠችው ድጋፍ ሳቢያ መሆኑን ደጋግመን አይተናል፡፡ይህ ክርክር እስከወዲያኛው የተዘጋ አይደለም በየጊዜው የሚነሳ ብቻ ሳይሆን እንደቀደመው ጊዜ ቀደም ሲል የተዋለ ውለታ እየተጠቀሰ መሻገር ፍጹም አይቻልም፤የጎደለውን ለይቶ ማስተካከል ያስፈልጋል፡፡
10ኛው መሪ ፕላን ከተማቱ በ2032 ተመራች ዓለም አቀፍ ከተማ የማድረግ ራዕይ ሰንቋል፡፡ይህን ራዕይ ዕውን ማድረግ የሚያስችሉ ግቦችና ተግባራት በየጥናት ርዕሱ በከተማ ልማት ፕላን መስክ የተሰማሩ ባለሙያዎች ያጠኗቸውን ፈንጠቂ ትናቶች መሰረት ተለይተው በስልታዊ ፕላኑ ተካትተው ተግባራዊ መሆን ጀምረዋል፡፡ የከተማ ፕላን ጉዳይ ስፓሺያል ጉዳ ብቻ አይደለም፤ ከሰው ልጅ አስተሳሰብ ጋር ቁርኝት ያላቸው ከመሬትና ከገጸ ምድር ጉዳዮች በላ የሆኑ እጅግ ጠናና ጉዳዮችን የሚይዝ ነው፡፡
ፕላኑም ልማቱም ለሰው እንጂ አልተዘጋጀምና የከተማዋን ልማት ከሰው ልጅ ልማት ነጥሎ ማየት ለውድቀት ራስን ማዘጋጀት ነው፡፡ በመሪ ፕላን ዝግት ወቅት ፈንጣቂ ጥነት ካቀረቡ ምሁራን መካከል ዶ/ር ምህረት ደበበና ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ይህነኑ ጉዳ አጽንኦት ሰጥተውታል፡፡ ቀደም ሲል የተዘጋጁት የከተማይቱ መሪ ፕላኖች ያለመተግበራቸው መንስኤ ሌሎች በርካታ ጉዳች የመኖራቸውን ያክል ሕዝቡ የከተማው ነዋሪ ማለት ነው ነባራዊ እና ህሊናዊ ሁኔታ ባግባቡ ተተንቶኖ የከተማ ፕላንና ልማት ፕላን ዝግጅትና ትግበራ መሠረት ማድረግ አለመቻሉ ነው፡፡ በመሪ ፕላን ዝግጅት ሰር አበርክሮምን የመሳሰሉ አለም ያጨበጨበላቸው ታዋቂ የከተማ ፕላን ባለሙያዎች ለአዲስ አበባ ፕላን አዘጋጅተዋል፡፡ ነገር ፕላኖቹ እንደታለመው ከተማዋን ማዘመን አልቻሉም ህዝቡንም ነዋሪ ማድረግ አልቻሉም ፤ለምን ብሎ መጠየቅ ለመፍትሄው ማንደርደሩ አይቀርምና ቀደም ሲል እንደተገለጸው ከበርካታ ጉዳች አንዱ ምን አልባት ቁልፍ ለሆነው ከተሜነት መፍጠር ትኩረት አለመነፈግ ያሻል፡፡
2.ነባራዊ ሁኔታ
ሀ. ምጣኔ ሀብታዊ ጉዳዮች
አዲስ አበበ ከተማ ሁሉም የሚኖርባት ናት ድሀው ሀብታሙ መካከለኛ ገቢ ያለውም የሚኖርባት ከተማ ናት፡፡ ምን አልባትም የሀገሪቱ አጠቃላ ማንነት የሚነበበው አዚሁ አዲስ አበባ ከተማ እንጂ ሌላ ሊሆን አይችልም ውለኛ ተመልካችም አጠኚም ካለ፡፡ በየትኛውም ዓለም እንዲህ አይነቱ የነዋሪዎች ኢኮኖሚያዊ ስብጥር እንግዳ አይደለም፡፡ ልዩ የሚሆነው ከተሞቹ ጉዳዩን ተቀብለው የሚያስተናግዱበት ሁኔታ ነው፡፡ በከተማቱ ለሚስተዋለው ድሕነት ዋነኛው መንስኤ ስራ አጥነት እንደሆነ የከተማ አስተዳደሩ ሪፖርቶች ያጠይቃሉ፡፡ ስራ አጥ ከሆት ዜጎቻችን መካከል የሚልቁት ወጣቶች ናቸው፡፡ የወጣቶች ስራ አተነት ችግር የመሆኑን ያክል በቴክኒክና ሙያ ስራ ዘርፎች በቀላሉ አሰልጥኖ ስራ መፈጠር ከተማቱንም ሆነ ሀገሪቱን ወደፊት ማራመድ የሚያስችል የሚያስጎመጅ ዕምቅ አቅም ነው፡፡ በዚህ ረገድ የከተማው አመራሮች ትልቁ ፈተና ከአመለካከት ጋር የሚያያዝ ችግር መሆኑ ይገለጻል፡፡ ስለዚህ ዋናው ጉዳይ ከተሜነት ላይ ያለ ችግር ነው ማለት ነው፡፡ (ከተሜነት ዘቅ ብለን እንበይነዋለን፡፡)
እንዲህ ዓይነቱ የጨለመ የሚመስል ዐውዳዊ ችግር ቢኖርም የጊዜን ሀብትነት የተረዱ ሳረፍደባቸው የሚሮጡ ትጉሃንም አሉ፡፡ የነዚህን ዘመኑን የዋጀ አመለካከት እርሾ አድርጎ ሌሎች የደነዘዙትን ዞ መውጠት የከተማው አመራር ቁለፍ ስራ ተደርጎ ሊታይ ይገባል፡፡
የከተማዋ ገቢም በየጊዜው እየጨመረ መምጣቱ ይታወቃል፡፡ እርግጥ ነው ዝቅ ብለን በምናነሳቸው ጉዳች ሳቢያ የውጪ ሀገር ቱሪስቶች ወደ ሀገራችን የሚገቡትም ሆነ የሚወጡት በዲስ አበባ በኩል ነው፤ይህን አጋጣሚ ተጠቅሞ ቆይታቸውን ማራዘም የሚያስችሉ ስራዎች እየተሰሩ አይደለምና ከዘረፉ መገኘት የሚገባውን ያክል መጠቀም አልተቻለም፡፡
ለ.ማኅበራዊ ጉዳዮች
አህጉር አቀፍና ዓለም አቀፍ ማዕከልነቱን ተከትሎ የማይኖርባት የዓለም ሕዝብ የለም ብሎ ደፍሮ መናገር ይቻላል፤የሀገሪቱ ሕሉም ብሔሮች የሚኖሩባት ትንሷ ኢትጵያ ናት፤በሀገሪቱ ሉ የሚባሉ ማሕበራዊ ተቋማትም እዚሁ አሉ-አዲስ አበባ! ይህ እንደተጠበቀ ሆኑ የሀገሪቱ ማኅበራዊ ሕጸጾች መፈልፈያና መስፋፊያ ከተማ ናት፡፡ ሲያድጉ ምን ይሆኑ ሆን በሚል ስጋት የሚታዩ ታዳጊዎች በከተማዋ ዋና ዋና አካባቢዎች ለምነው ባገኙት ገንዘብ ማስቲሽ ሲስቡ ማየት ብርቅ አይደለም፤ ሴተኛ አዳሪነትና መሰል ችግሮችም በከተማዋ የሚስተዋሉ ሕጸጾች ናቸው፡፡ ሱሰኝነት ስካር በየቦታው መጸዳዳት እጅግ የተለመደ በመሆኑ ማንም ነገሬ ሲለው ኤስተዋልም፡፡
ሐ.መሰረተ ልማት
በበቂ ዝግጅትና በቅንጅት የሚሰሩ እንዳልሆኑ የሚተቹ የመሠተ ልማት ዝርጋታዎች የፌዴራሉም ሆነ የከተማ አስተዳደሩ የኩራትና የስኬታማነት መገለጫ ተደርገው ይነሳሉ፡፡ ለመሠረተ ልማት ዝርጋታዎች ትኩረት ነፍጓል የሚል ክስ ንፉግነት ነው፤ በዚህ ረገድ መንግስትን ማወደስ ተገቢ ነው፤ክሱ ሊሆን የሚገባው በበቂ ጥናት አለመሰራታቸው፣ቅንጅት አለመኖሩ፣የጥራት መጓደልና የመሳሰሉት ጉዳዮች ናቸው፡፡
መ. የሳሳ ከተሜነት
ከተሜነት ስልጣኔ ነው፣ስልጣኔ ደግሞ ህግ አክባሪነት ነው፡፡ ሌሎች ጉዳዮችም የከተሜነት መገለጫ ባሕሪያት አሉ፡፡ ለጊዜው ሌሎችን እንተዋቸውና ሕግ አክባሪነት ምርኩዝ አድርገን የከተማችንን ነዋሪዎች ማንነት እንፈትሽ፤ ማንነት ዘርፉ ብዙም አይደል! ህግ አክባሪነት የአካባቢ ንጽህና መጠበቅ ነው፡፡ እንደ አዲስ አበባ ባደባባይ የሰው ልጅ ያለዕፍረት የሚጸዳዳበት ከተማ ይኖር ይሆን፡፡ ሕጉ ስርዓቱ እያለ ህግ አስከባሪው አይቶ እንዳለየ ያልፋል፡፡ የዚህ ኣነቱ አስነዋሪ ድርጊት በዚሁ ከቀጥለ የሀገሪቱን ገጽታ ያበላሻል፡፡ ሌላው ህግወጥነት የሚስተዋለው በአስከርካሪዎች ነው፡፡ ከተፈቀደው የፍጥነት ወሰን በላይ ማሽከርከር በጡሩምባ ድምጽ አካባቢን በድምጽ መበከል ለእግረኛ ቅደሚያ መንፈግ የአሽከርካሪዎቻችን መለያ ባሕሪያት ናቸው፤ በዚህ የተነሳም የበርካቶች ውድ ህይወት እየተቀጠፈ አካል እየጎደለም ነው፡፡ ይህ ደግሞ አዲስ አበባ ከተማን የምትፈራ ከተማ አድርጓታል፡፡
ከላይ የተተቃቀሱት ችግሮች የከተማውን አመራር አስተውሎት የሚሹት መፈታት መገባቸው ችግሮች ናቸው፡፡ ከሕግ አክባሪት ጋር የተያያዙትን ችግሮች ሕዝቡን በተለያዩ የተግባቦት መሳሪዎች በመድረስ ማረም ይቻላልና የዚህ ዕቅድ ትኩረትም እዚሁ ላይ ይሆናል፡፡
3.ዓላማ፡
የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የከተሜነት ባሕርይ በማጎልበት ከተማዋን ለኑሮና ለስራ ምቹ ማድረግ
4.ግብ
የከተማዋን ነዋሪዎች የከተሜነት ባሕርይ ማጎልበት የሚያስችሉ የተግባቦት ስራዎች መስራት
በተግባቦት መለወጥ የሚገባቸው
ሀ. በየመንገዱ መጸዳዳት
ለ.ግብታዊ አሽከርካሪነት
የዚህ ዓይነቱ ተግባራት ፈጻሚዎች
በአመዛኙ ወጣት ወንዶች ናቸው
5.መለያ ባህርያቸው
ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ባለባቸው አካባቢ መሄድ ያዝወትራሉ(ምሳሌ፣ ስታዲየም ፣ መስቀል አደባባይ፣ሰባ ደረጃ፣ስፖርት ባሮች)
ፊልምና መሰል መዝናኛቸው ነው( ምሳሌ ሲኒማ ቤቶች፣ሆቴሎች )
የህዝብ ግንኙነት መሳሪያዎች
1.ቢል ቦርድ( መስቀል አደባባይ፣ ስታዲየም፣ስድስት ኪሎ፣ጃን ሜዳ)
2.የማስታወቂያ ቁሳቁሶች(ቲሸርት፣ኮፍያ፣ ፍላሽ ካርድ)
3.ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች እና ሌሎች የመዝናኛ ሁነቶች
4.የቴሌቭዢን ማስታወቂያዎች
6.የድርጊት መርሀ-ግብር
ተ.ቁ. የሚሰሩ ስራዎች መለኪያ ብዛት ምርመራ
1 ቢል ቦርድ በቁጥር 6
2 ቲሸርት በቁጥር 120000
3 ፍላሽ ካርድ በቁጥር 300000
4 ኮፍያ በቁጥር 300000
5 ሁነት በሁነት ቁ. 8
6 ስቲከር
7 ቢዝነስ ካርደ
8 ድረ-ገጽ
9 ብሮሸር
10 ስክሪን ሴቨር
11 የቴሌቭዢን ማስታወቂያዎች 2
12 ባግ
13 ከረጢት
14 ፕሬስ ኪት
መሪ ቃል
ወንዶች ከተሜ ናቸው፤ከተማቸውን ይንከባከባሉ!!!